ዋናኛ ገጽ (ወደ መነሻ ገጽ ይመለሱ > ስለ ቤጂንግ ፎሪየን ስተዲስ ዩኒቨርሲቲ > የዩኒቨርሲቲው ገፅታ

ቤተ መጻሕፍት

ዩኒቨርሲቲው ልሳነ ብዙ አለም አቀፍ የሰነድ ንብረት ማዕከል ገንብቷል። የቤተ መፃህፍቱ የወረቀት ሰነዶች ስብስብ በ107 ቋንቋዎች የተጻፉ ሲሆን ወደ 1.6 ሚሊዮን የሚጠጉ ናቸውከ1.41 ሚሊዮን በላይ የኤሌክትሮኒክስ መጽሃፎች፣ 873 የወረቀት ጋዜጦች እና ወቅታዊ ጽሑፎች እና 103 የመረጃ ቋቶች አለው። ቋንቋ፣ ስነ-ጽሁፍ እና ባህልን እንደ ዋና ሰነዶች የያዘ ክምችት ነው።

ከቅርብ ዓመታት ወዲ የትምህር መሥኮችን በማሳደግ፣ ፖለቲካ፣ በኢኮኖሚ፣ በዲፕሎማሲ፣ በሕግ በዜና፣ በአስተዳደር፣ በአገራዊ እና በክልላዊ ጥናቶች ዙሪያ ያሉ ጽሑፎችን ቀስ በቀስ የሚሰበሰቡበትን ሥርዓት ፈጥሮ እያሰባሰበ ይገኛል። ዩኒቨርሲቲው ተደራሽ፣ የተሳለጠ፣ ብቁ፣ በአዳዲስ ፈጠራዎች የታገዘ እና የተቀናጀ የመረጃ መዋቅር በመገንባት የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጅዎችን መጠቀሙን ቀጥሏል፡፡ በተጨማሪም የሶፍትዌር መስኮችን በማዳበር እንደ የባለ ብዙ ቋንቋ ኦፊሴላዊ ድረ-ገጽ፣ ስማርት የምዝገባ መድረክ፣ የመረጃ ማዕከል እና የመስመር ላይ የማስተማር እና የማስተማር ግብአት መድረኮችን አዘጋጅቷል። ፈጠራን እና እድገትን ለማመቻቸት አስተውሎታዊ የማስተማሪያ አካባቢዎችን እና ለመምህራን ሥራ የሚያግዙ ዘመናዊ የማስተማሪያ መሳሪያዎችን እና ቤተ ሙከራዎችን በመገንባት አስደናቂ ውጤት አስመዝግቧል። BFSU የትምህርት ሚኒስቴር የመምህራንን ልማት ሰው ሰራሽ አስተውሎት ለማሳደግ ለተቀረፀው  የሙከራ ፕሮጀክ ከተመረጡ መጀመሪያዎቹ ዩኒቨርሲቲዎች አንዱ ሆኗል፡፡ የቋንቋን አጀማመር፣ አሁን የደረሰበትን ደረጃና ባህል ለማሳየት የሚያስችል ዘመናዊ የዓለም ቋንቋዎች ቤተ መዘክር እንዲሁም BFSU ታሪክ ሙሉ ለሙሉ የሚዘክር አዲስ የታሪክ ሙዚየም አቋቁሞ ለተጠቃሚዎች ክፍት አድርጓል፡፡


ቤተ መፃህፍቱ ባለ ስድስት ወለል ሆኖ አጠቃላይ 23,000 ካሬ ሜትር ስፋት ያለው ፎቅ ነው። በውስጡም 2,200 በላይ የንባብ መቀመጫዎችን18 የጥናት ክፍሎችን የአካዳሚክ ትምህርት አዳራሾችን የአካዳሚክ ሴሚናር አዳራሾችን የስልጠና ክፍሎችንወዘተ. የያዘ ነው፡፡  በተጨማሪም የኤግዚቢሽን አዳራሾችን፣ የመምህራን መጽሃፍ ቤቶችን፣ የተማሪዎች መጽሃፍ ካፌን የሚያስደምሙ የቋንቋ እና የባህል ማዕከላትን እና ሌሎች የባህል እና የመዝናኛ ቦታዎችን ይዟል

ቤተ መፃህፍቱ በሙሉ በገመድ አልባ የመረጃ መረብ የተሸፈነ ሲሆን 24 ሰዓት የግል የሚከናወን    የመጽሐፍ መመለሻ አገልግሎት መስኮት አለው። የተለያዩግል አገልግሎት መሳሪያዎችን ማለትም የግል ፍቶ ኮፒ ፣ ማተም፣ ስካን ማድረግ የሚያስችሉ፣ መፅሃፍ መበደር እና መመለስ፣ ኤሌክትሮኒካዊ ዳሰሳ፣ ኤሌክትሮኒካዊ ጋዜጣ ንባብ እና የመሳሰሉትን አገልግሎቶችን የማንም እገዛ ሳያስፈልግ ማግኘት የሚያስችል ሆኖ የተደራጀ ነው፡፡ በተጨማሪም የኤሌክትሮኒክስ የማንበቢያ ቦታ፣ የመልቲሚዲያ የመማሪያ ቦታ እና በሁሉም ቦታ የሚታይ የመረጃ ማስላለፊያ ስርዓት አለው።

BFSU ቤተ መፃህፍት "የውጭ፣ የተለዬ ትክክለኛ እና ሁሉን አቀፍ" የሚለውን የዩኒቨርሲቲውን የትምህርት ፍልስፍና ያከብራል፡፡ ሰዎች ተኮር መርሃ ግብር እናእውቀትኢኮኖሚ እናዲጂታል ልማት ፈጣን እንቅስቃሴ ጋር የሚስማማ ነው። ለአንባቢዎች በበለጸጉ የመሰብሰቢያ ግብዓቶች፣ ምቹ የመማሪያ አካባቢ፣ ሰብአዊነት የተላበሰ የአገልግሎት ጽንሰ-ሀሳብ እናከፍተኛ የአገልግሎት መስጫ ተቋማት የተሟላ የመረጃ አገልግሎቶችን እና አካዳሚያዊ ድጋፎችን

ይሰጣል። በተመሳሳይ የውጭ ቋንቋ አካዳሚያዊ እና የተለዩ ሀብቶችን ለማከማቸት ቁርጠኝነት ያለው ነው፡፡ ለዚህም በዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ እና በመካከላቸው ያሉ በርካታ ባህሎችን ለማዋሃድ የሚያስችል የመረጃ ማዕከል እና የባህል ልውውጥ ማዕከል በመሆን እያገለገለ ይገኛል፡፡