ዋናኛ ገጽ (ወደ መነሻ ገጽ ይመለሱ > ዜና

ከቤጂንግ ፎሪዬን ስተዲስ ዩኒቨርሲቲ የተውጣጡ የውጭ ሀገር መምህራን ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀንን ለማክበር ለቻይናውያን እና ለውጭ ሀገር ሴቶች በተዘጋጀው የግብዣ ሥነ ሥርዓት ላይ ተገኝተዋል።

Updated: 2026-03-17

እኤአ መጋቢት 6 ቀን 2026፣ ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን የቻይና እና የውጭ አገር ሴቶች በተገኙበት በታላቅ ዝግጅት በቤጂንግ ተከብሯልበሥነ ሥራዓቱ ላይ ቻይና መንግስት ምክር ቤት አባል እና የመላው ቻይና የሴቶች ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት ቼን ይን ንግግር አድርገዋል።

በበዓሉ ላይ ከሚመለከታቸው የማዕከላዊ ኮሚቴ እና ከመንግስት አካላት የተውጣጡ ባለስልጣናት፣ ሴት ተወካዮች እና የብሔራዊ ሕዝባዊ ኮንግረስ እና የቻይና ሕዝባዊ የፖለቲካ ምክክር ኮንፈረንስ አባላት፣ ከሁሉም የኑሮ ደረጃ እና ከሁሉም ብሄረሰቦች የተውጣጡ ታዋቂ ሴት ተወካዮች፣ ከሆንግ ኮንግ እና ማካ የተውጣጡ የሴቶች ተወካዮች፣ የቻይና ዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ ተወካዮች፣ በቻይና የሚገኙ ዓለም አቀፍ ድርጅቶች ተወካዮች እና ከአንድ ሺህ በላይ የቻይና እና የውጭ አገር እንግዶች ተገኝተዋል። ከቤጂንግ ፎሪን ስተዲስ ዩኒቨርሲቲ የተውጣጡ አስራ አንድ የውጭ ሀገር ሴት መምህራን በሥነ ሥርዓቱ ላይ እንዲገኙ ተጋብዘው ተካፋይ ሆነዋል