እኤአ የካቲት 28 ቀን 2026 ሁሉም የBFSU አመራሮች በተገኙበት የዩኒቨርሲቲውን የ2026 የጸደይ ሴሚስተር ዕቅድ ለማውጣት በYifu ህንፃ ውስጥ ስብሰባ ተካሂዷል። በስብሰባው ላይ የፓርቲው ፀሐፊ ፕሮፌሰር ሊ ሃይ እና የፓርቲው ምክትል ፀሐፊ እና የዩኒቭርሲቲው ፕሬዝዳንት ፕሮፌሰር ጂያ ዌንጂያን የዩኒቨርሲቲውን የአዲሱን ዓመት የተለያዩ የተግባር ዕቅዶችን በቅደም ተከተል ዘርዝረዋል።

ፕሮፌሰር ሊ ሃይ ዓለም አቀፍ ትብብርን አስመልከተው ሲናገሩ ዩኒቨርሲቲው እንደ ዓለም አቀፍ ቋንቋዎች፣ ባህሎች እና አስተዳደሮች ባሉ ቁልፍ ዘርፎች ላይ ማተኮር እንዳለበት እና በሩን ለውጭው ዓለም ክፍት በማድረግ እና ዓለም አቀፍ ግንኙነቶችን የመፍጠር ጥረቱን ማስተባበር አለበት ብለዋል። ዩኒቨርሲቲው በተጨማሪም የቻይና-የውጭ ሀገራት የትብብር ትምህርት ፕሮግራሞችን ጥራት እና ቅልጥፍና ለማሻሻል በዓለም ታዋቂ ከሆኑ ዩኒቨርሲቲዎች ጋር በከፍተኛ ደረጃ እና በተለያዩ ዘርፎች በንቃት መሳተፍ አለበት። BFSU የኮንፊሽየስ ኢንስቲትዩቶችን ልማት በብቃት በማሳደግ ታዋቂና ገናና ስሙን የጠበቀ የባህል ማስፋፋትን ለማሳደግ "የቻይና ድልድይ" እንደተሰኘው ፕሮግራም ባሉ ልዩ የውድድር ፕሮግራሞች ውጤታማ በሆነ መንገድ ያስፈጽማል በማለት አክለዋል፡፡ ፕሮፌሰር ጂያ ዌንጂያን በበኩላቸው BFSU ለአለም አቀፍ ትብብር አዳዲስ አድማሶችን በመክፈት፣ SOAS ከተሰኘው የለንደን ዩኒቨርሲቲ ጋር ያለውን የትምህርት ትብብር ፕሮግራም በተቀላጠፈ ሁኔታ ተግባራዊ ማድረግና ሙሉ በሙሉ ማሳደግ፣ ለአለም አቀፍ የትብብር ትምህርት አዲስ ሞዴል መፍጠር፣ ለኮንፊሺየስ ተቋማት አዲስ መድረክ እና "111 የባለመያዎች ቅጥር መሠረቶች" ለተሰኘው ፕሮጄክት አዲስ መቹ ሁኔታን ለመፍጠር፣ ጥሩ የረጅም ጊዜ እቅዶችን ማዘጋጀትና ተግባራዊ ማድረግ ያሰፈልጋል፡፡ ብሔራዊ ስትራቴጂዎችን በንቃት ለማገልገል፣ ከፍተኛ ጥራት ያለው የትምህርት ትብብር ልማትን ማሳደግ እና "ትምህርት በቻይና" የሚለውን ታዋቂ መለያ ስም እና የአቅም ግንባታ ማራመድ አስፈላጊ መሆኑን ተናግረዋል።