ዋናኛ ገጽ (ወደ መነሻ ገጽ ይመለሱ > ዜና

የኡራጓይ ፕሬዝዳንት አማንዱ ኦርሲ ቤጂንግ ፎሪዬን ስተዲስ ዩኒቨርሲቲን ጎበኙ

Updated: 2026-03-17

እኤአ የካቲት 4 ቀን 2026 የኡራጓይ ፕሬዝዳንት አማንዱ ኦሲ ቤጂንግ ፎሪን ስተዲስ ዩኒቨርሲቲ (BFSU) ጎብኝተዋል። የBFSU ፓርቲ ኮሚቴ ፀሐፊ ፕሮፌስር ሊ ሃይ፤ የፓርቲ ኮሚቴ ምክትል ፀሐፊ እና የBFSU ፕሬዝዳንት ፕሮፌስር ጂያ ዌንጂያን፤ የፓርቲ ኮሚቴ ቋሚ ኮሚቴ አባል እና የBFSU ምክትል ፕሬዝዳንት ፕሮፌስር ዣኦ ጋንግ፤ በኡራጓይ የቻይና አምባሳደር ሁዋንግ ያዞንግ፤ ቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የላቲን አሜሪካ እና የካሪቢያን ጉዳዮች መምሪያ ሃላፊ ዣንግ ዌንዌይ፤ እና የትምህርት ሚኒስቴር የዓለም አቀፍ ትብብር እና ግንኙነት መምሪያ ምክትል ዳይሬክተር ዣንግ ጂን በዝግጅቱ ላይ ተገኝተዋል።

ፕሬዝዳንት ሲ ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት ሲሆን የቀድሞው የኡራጓይ ፕሬዝዳንት ሙጂካ  በ2013 በተከሉት የቻይና-ኡራጓይ የወዳጅነት ዛፍ ተገኝተው ፕሮፌስር ሊ ሃይ እና ፕሮፌስር ጂያ ዌንጂያን ጋር በመሆን ዛፉ አፈር በማሰታቀፍ ውሃ አጠጥተዋል፡፡ አዲሱን የወዳጅነት ዛፍ መግለጫ ሰሌዳ ፍተዋልፕሮፌስር ሊ ሃይ ለፕሬዝዳንት ኦርሲ የወዳጅነት ዛፉን የምስክር ወረቀት ሰጥተዋል

ይህንን ተከትሎ ፕሬዝዳንት ሲ እና የልዑካን ቡድናቸው የንኋ አዳራሽን ጎብኝተው የስፓኒሽ ቋንቋ ትምህርት የሚሰጡ ከ16 ዩኒቨርሲቲዎች እና ከቤጂንግ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የመጡ መምህራን እና ተማሪዎች ጋር ተገናኝተው ተወያይተዋልሥነ ሥርዓቱ የተመራው በፕሮፌስር ጂያ ዌንጂያን ነበር

በስብሰባው ላይ ፕሮፌስር ሊ ሃይ ቤጂንግ ፎሪን ስተዲስ ዩኒቨርሲቲን (BFSU) በመወከል ለፕሬዝዳንት ኦሲ የእንኳን ደህና መ ንግግር አድርገዋል። BFSU ከኡራጓይ ጋር ያለውን የቅርብ ትብብር ሁልጊዜ እንደሚያጠናክር ገልፀው የሁለቱንም ሃገራት ቋንቋዎችና ባህሎችን የሚያውቁ በቻይና እና በኡራጓይ መካከል ወዳጅነትን የሚያጎለብቱ ወጣት አምባሳደሮችን ለማፍራት ከኡራጓይ ዩኒቨርሲቲዎች እና ከአካዳሚክ ተቋማት ጋር ጠንካራ ግንኙነት እና ትብብር ለማድረግ ያላቸውን ቁርጠኝነት ገልፀዋል።

ፕሬዝዳንት ባደረጉት ንግግር በአገሮች መካከል ጤናማ እና የተረጋጋ ግንኙነት እንዲኖር ዋነኛው ጉዳይ የጋራ መተማመን እንደሆነ እና የአካዳሚክ ግንኙነቶችም ትልቅ ሚና እንደሚጫወቱ ገልፀዋል። በቻይና እና ኡራጋይ እንዲሁም በቻይና እና በላቲን አሜሪካ መካከል ያሉት የአካዳሚክ ግንኙነቶች ጥልቅ የትብብር ደረጃን የሚወክሉ ከመሆናቸውም በላይ የሕዝብ ለሕዝብ ትስስርን ለማጠናከር መሰረት የሚጥሉ ናቸው። ሁለቱም ወገኖች እርስ በእርሳቸው ከተሞክሮዎቻቸው መማር፣ የእውቀት ምሁራዊ ውስንነቶችን ስወገድ እንዳለባቸውና በጋራ መተባበር እና በመነጋገር ሰላምን እና ልማትን ማበረታታት እንደሚችሉ ያላቸውን ተስፋ ገልጸዋል።

ፕሬዝዳንት ከንግግራቸው በኋላ በዝግጅቱ ላይ ከተገኙት መምህራንና ተማሪዎች ጋር ተወያይተዋልፕሮፌስር ሊ ሃይ የBFSU መምህራንና ተማሪዎችን ወክለው ለፕሬዝዳንት ኦሲ በBFSU የስፓኒሽና የፖርቱጋል ትምህርት ቤት ተማሪዎች የሳሉትን የቻይናና የኡራጋይን ወዳጅነት የሚያሳይ ዛፍ ሥዕል ለፕሬዝዳንት ኦሲ አበርክተዋል።

ዝግጅቱ ከመጀመሩ በፊት ፕሬዝዳንት BFSU የስፓኒሽ ቋንቋ ትምህርት ፕሮግራም ስኬቶችን የሚያሳይ ኤግዚቢሽን ጎብኝተው አስተያየታቸውን በፅሁፍ አስፍረዋል። ከዚያም BFSU የስፓኒሽ ቋንቋ ፕሮግራም የተውጣጡ ተማሪዎች ሙዚቃ ያቀረቡ ሲሆን ተመልካቾች አድናቆታቸውን በጋለ ጭብጨባ ገልፀውላቸዋል

የኡራጓይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሉቤቴኪን፣ ቻይና የኡራጓይ አምባሳደር ካብራል፣ የእንስሳት እርባታ፣ የግብርና እና የአሳ ሀብት ሚኒስትር ፍራቲ፣ የኢንዱስትሪ፣ የኢነርጂ እና የማዕድን ሚኒስትር ካርዶና እና ሌሎች የልዑካን ቡድኑ አባላት በዝግጅቱ ላይ ተሳትፈዋል።