ዋናኛ ገጽ (ወደ መነሻ ገጽ ይመለሱ > ዜና

በቻይና የኡራጓይ አምባሳደር አኒባል ካብራል ቤጂንግ ፎሪዬን ስተዲስ ዩኒቨርሲቲን ጎበኙ፡፡

Updated: 2026-01-12

ዲሴምበር 24 ቀን2025፣ በቻይና የኡራጓይ አምባሳደር አኒባል ካብራል ቤጂንግ ፎሪዬን ስተዲስ ዩኒቨርሲቲን ጎብኝተዋል። በዚህ ጊዜ የBFSU ፕሬዝዳንት እና የዩኒቨርሲቲው የኮሚኒስት ፓርቲ ምክትል ፀሐፊ ፕሮፌስር ጂያ ዌንጂያን እና የፓርቲው ኮሚቴ ቋሚ ኮሚቴ አባል እና ምክትል ፕሬዝዳንት ፕሮፌስር ዣኦ ጋንግ ካብራልን እና የልዑካን ቡድናቸውን ተቀብለው አነጋግረዋል፡፡

በጉብኝቱ ወቅት ፕሬዝዳንት ጂያ ዌንጂያን የቤጂንግ ፎሪዬን ስተዲስ ዩኒቨርሲቲ (BFSU) በአካዳሚክ እድገት፣ በዓለም አቀፍ ግንኙነት፣ በስፓኒሽ ቋንቋ ፕሮግራም እና በላቲን አሜሪካ ጥናቶች ረገድ ያለበትን መሰረታዊ ሁኔታ አስተዋውቀዋል። በተጨማሪም በBFSU እና በኡራጓይ መሪዎች እና በዩኒቨርሲቲ ባልደረቦች መካከል ያለውን ልባዊ ግንኙነትና እና መስተጋብር ዳሰዋል። BFSU ከኡራጓይ እና ከሌሎች የላቲን አሜሪካ አገራት ጋር ለሚደረጉ ግንኙነቶች ትልቅ ጠቀሜታ እንዳለው እና በሁለቱ ሀገራት መካከል የሚኖረው መልካም ግንኑነት በትምህርት ትብብር እና በወጣቶች ልምድ ልውውጥ ረገድ በመግባባት እና በወዳጅነት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተስፋ እንደሚያደርጉ ተናግረዋል።

ካብራል ቤጂንግ ፎሪዬን ስተዲስ ዩኒቨርሲቲን እንደገና ለመጎብኘት በመቻላቸው የተሰማቸውን ደስታ ገልጸዋል። ዩኒቨርሲቲው ዓለም አቀፍ ተሰጥኦዎችን በማዳበር እና የባህል ልውውጥን በማስፋፋት ረገድ ያለውን ጉልህ ሚና ከልብ አድንቀዋል። ወደፊት በሁለቱ ወገኖች መካከል ያለውን ትብብር ለማጠናከር፣ የወጣቶችን ግንኙነት እና የአካዳሚክ እንቅስቃሴዎችን ለማካሄድ፣ በሁለቱ አገራት መካከል የትምህርት እና የባህል መስተጋብርን ለማሳደግ እና በሁለትዮሽ ግንኙነቶች ውስጥ አዲስ ጥንካሬን ለመፍጠር ያላቸውን ጉጉት ገልፀዋል።