ዋናኛ ገጽ (ወደ መነሻ ገጽ ይመለሱ > ዜና

አምስተኛው የዓለም አቀፍ የውጭ ጥናት ዩኒቨርሲቲዎች የፕሬዚዳንቶች ፎርም በሀንጆኡ ተካሄደ፡፡

Updated: 2025-11-03

በቤጂንግ ፎሪየን ስተዲስ ዩኒቨርሲቲ (BFSU) እና በጂያንግ ዓለም አቀፍ ጥናት ዩኒቨርሲቲ የተዘጋጀው አምስተኛው ዓለም አቀፍ የውጭ ጥናት ዩኒቨርሲቲዎች የፕሬዚዳንቶች ፎርም(GAFSU) ጥቅምት 24 ቀን በሀንጆኡ ተካሂዷል።

በውይይት መድረኩ ከ24 የህብረቱ አባል ተቋማት የተውጣጡ አመራሮች ተሳታፊ ሆነዋል። ከእነዚህም መካከል ቻይና የአለም አቀፍ ትብብር ማህበር ፕሬዝዳንት እና የቀድሞው ቻይና የትምህርት ሚኒስትር ም/ሚንስትር ሊዩ ሊሚን  የGAFSU ሊቀመንበር፣ የBFSU ፕሬዝዳንት እና የBFSU የኮሚኒስት ፓርቲ ኮሚቴ ምክትል ፀሀፊ የሆኑት ጂያ ንጂያን፣  የGAFSU ቦርድ አባል እና የጂያንግ ዓለም አቀፍ ጥናቶች ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ንግ ሁዋንጆው እና ሌሎች አመራሮች በፎርሙ ላይ ተገኝተዋል።

"የወደፊት መፍትሄዎች፣ የሰው ሰራሽ አስተውሎትን ማጎልበት፣ የተቀናጀ ልማት" በሚል መሪ ቃል 27 አገሮች የሚገኙ፣ ከ60 በላይ ዩኒቨርሲቲዎችና ተቋማት የተውጣጡ ከ170 በላይ ዓለም አቀፍ ባለሙያዎችና ሁራን በፎርሙ ላይ ተገኝተዋል። ፎርሙ "በዲጂታል ኢንተለጀንስ ዘመን በቋንቋ ትምህርትና ምርምር ውስጥ የፈጠራ ሥራን በትብብር ለማሳደግ የሚኖረውን ተነሳሽነት" አ አሳይቷል