ዋናኛ ገጽ (ወደ መነሻ ገጽ ይመለሱ > ዜና

የቡልጋሪያ ምክትል ፕሬዝዳንት ኢሊያና ዮቶቫ BFSUን ጎበኙ።

Updated: 2025-10-17

እ.ኤ.አ. ኦክቶበር 15፣ 2025 የቡልጋሪያ ምክትል ፕሬዝዳንት ኢሊያና ዮቶቫ ቤጂንግ ፎሪየን ስተዲስ ዩኒቨርሲቲን ጎብኝተዋል። የ BFSU ፕሬዝዳንት እና የዩኒቨርሲቲው ፓርቲ ኮሚቴ ምክትል ፀሃፊ ጂያ ዌንጂያን ከዮቶቫ እና ልዑካን ቡድናቸው ጋር ተገናኝተዋል።

የዩኒቨርሲቲው ፕሬዘዳንት ጂያ ዌንጂያን BFSU ለም አቀፍ ግንኝኙነቶችን፣ የተማሪዎችን ሥልጠና እና የባለብዙ ወገን ዲሲፕሊን ውህደት ልማት መስክ የቅርብ ጊዜ ስኬቶችን አስተዋውቀዋል። ፕሬዘዳንቱ በንግግራቸው BFSU ለቡልጋሪያኛ ቋንቋ ፕሮግራም እና ዲሲፕሊን እድገት ትልቅ ትኩረት እንደሚሰጥ ገልፀው የቡልጋሪያ መንግስት እና በቻይና የሚገኘው የቡልጋሪያ ኤምባሲ BFSU የሚያደርጉትን ድጋፍና እገዛ አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተስፋ እናደርጋለን ብለዋል። BFSU ሁለቱ ሀገራት ወጣት ሁራን መካከል ትብብሮች እና ግንኙነቶችን በንቃት ማስተዋወቅ እና የሁለቱን ህዝቦች ወዳጅነት ለማሳደግ የበኩሉን አስተዋፅኦ ለማድረግ ቋንቋን የድልድይነት ጥቅሞ ሙሉ በሙሉ ለመጠቀም በትጋት ይሠራል በማለት ነግግራቸውን ደምድመዋል የቡልጋሪያ ምክትል ፕሬዝዳንት ዮቶቫ በበኩላችው ሰብአዊነት ልማትን አስፈላጊነት አፅንዖት ሰጥተው ወደፊት በሁለቱ ሀገራት ተማሪዎች እና ምሁራን መካከል ተጨማሪ ትብብሮች እና ግንኙነቶችን እንደሚጠናከሩ ያላቸውን ዕምነት ገልፀዋል። የቡልጋሪያ መንግስት ከBFSU ጋር በመተባበር የሁለቱን ህዝቦች ወዳጅነት በትምህርት ትብብር በኩል ለማጠናከር ፈቃደኛ መሆኑን አስገንዝበዋል

ምክትል ፕሬዝዳንት ዮቶቫ ከዩኒቨርሲቲው ፕሬዘዳንት ጋረ ያደረጉትን ስብሰባ ጨረሱ በኋላ ለBFSU መምህራን እና ተማሪዎች ንግግር ማድርጋቸውም በላይ ከታዳሚዎቹ ጋር ውይይት አካሂደዋል።

በዝግጅቱ ላይ ምክትል ፕሬዝዳንቷ በBFSU የቡልጋሪያ ጥናት ማእከል ልዩ ተመራማሪ የሆኑትን ማ ሲፑን የቡልጋሪያን ታሪክ እና ባህል በቻይና እንዲስፋፋ ላደረጉት የላቀ አስተዋፅዖ በማመስገን የቡልጋሪያ ሪፐብሊክ የቅዱስ ሲረል እና የቀዱስ መቶድየስ የመጀመሪያ ደረጃ ሜዳሊያ ሸልመዋቸዋል።